February 03, 2026
February 04, 2026
Dire Dawa Administration Council
የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫም የም/ቤቱ የተሻሻለው የአሰራር እና የአባላት ስነምግባር ደንብ ቁጥር 39/2015 አንቀጽ 13 መሠረት የም/ቤቱ መደበኛ ጉባኤ በአመት ቢያንስ 2ጊዜ እንደሚካሄድ እንደሚገልጽ ጠቅሰው የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ አመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 26 እስከ 27/2018 ድረስ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
በጉባኤውም ም/ቤቱ የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን የሚሰጥ ይሆናል። በመሆኑም የጉባኤው አጀንዳዎች የም/ቤቱን የ3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ አመት 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ቃለጉባኤን ማጽደቅ ፣ የአስተዳደሩ የአስፈጻሚ አካላት እና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያው ግማሽ አመት አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ ፣ የተለያዩ አዋጆችን ማጽደቅ እንደሚሆኑ የተከበሩ አፈጉባኤው ጠቅሰው የም/ቤቱ አባላትም በጉባኤው ላይ በመገኘት ከህዝብ የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#መረጃ | ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት እነዚህን አማራጮች ይጠቀሙ ⬇️
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት መረጃዎችን ለማግኘት እነዚህን የማህበራዊ ትስስር ገፆች በመከተል አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ!
ድህረ-ገጽ [Website]
www.ddacouncil.gov.et
ፌስቡክ [Facebook]
https://www.facebook.com/profile.php?id=100067680782694&mibextid=LQQJ4d
ዩቲዩብ [YouTube]
https://youtube.com/@diredawaadministrationcouncil?si=TB3KelHlFoN6FhsP
ቲክ ቶክ [Tik Tok]
https://www.tiktok.com/@dire.administrati?_t=8rV9o39Vegq&_r=1
ቴሌግራም [Telegram]
ለተመራጭ የምክር ቤት አባላት ብቻ፤
ስለ አብሮነትዎ እናመሰግናለን!
ይህን አጋራ