የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አብዲ ሙክታር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫም የም/ቤቱ የተሻሻለው የአሰራር እና የአባላት ስነምግባር ደንብ ቁጥር 39/2015 አንቀጽ 13 መሠረት የም/ቤቱ መደበኛ ጉባኤ በአመት ቢያንስ 2ጊዜ እንደሚካሄድ እንደሚገልጽ ጠቅሰው የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ አመት 11ኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 26 እስከ 27/2018 ድረስ እንደሚካሄድ ገልጸዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 4ኛ አመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 28 እስከ 29/2017 ዓ.ም በምክር ቤቱ የመሠብሠቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 2 :00 ሰአት ጀምሮ ይካሄዳል። በጉባኤውም የተለያዩ አጀንዳዎች የሚቀርቡ ሲሆን ለአብነት ያህልም የአስፈጻሚ አካላት እና ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት የ2017 በጀት አመት የ6 ወራት አፈጻጸም ማጽደቅ ፣ ሹመቶችን ማጽደቅ እንዲሁም የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቶ የሚያጸድቅ ይሆናል። የተከበራችሁ የምክር ቤት አባላትም በእለቱ ተገኝታችሁ የጉባኤው ተሳታፊ እንድትሆኑ መልእክቴን አስተላልፋለሁ ። ፈቲህያ አደን
ሰንደቅ ዓላማችን የሉዓላዊነታችን መገለጫ፤ የአብሮነታችን አርማ!
የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን ጋዜጣዊ መግለጫ
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ኛ የስራ ዘመን 3ኛ አመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ